• +251462204629
  • Hawassa , Ethiopia

የፋይናንስ ቢሮ ስልጣንና ተግባር

home-bg1
  1. የክልሉን መንግስት በጀት ማዘጋጀት፣ በተፈቀደው በጀት መሠረት ክፍያ መፈጸም፣ የበጀቱን አፈጻጸም ማስተዳደር፣ መገምገምና መቆጣጠር፤
  2. የክልሉ መንግስት የበጀት፣የሂሳብ፣የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥራዓት መዘርጋትና በስራ ላይ እንዲውል ማድረግና መከታተል፤
  3. የክልሉን መንግስት የገንዘብ ሰነዶች፣ ገንዘቦችና ንብረቶች መያዝና ማስተዳደር ይገኙበታል፡፡
  4. የክልሉ መንግስት የብድርና እርዳታ ስምምነቶችን መፈራረምና ማስተዳደር፤
  5. በኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ስራ ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ማስተባበርና መቆጣጠር፤
  6. የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች የብቃት ምዘና ማድረግ፣ የስራ ውል መፈራረም፣ ማስተባበር፣ መከታታልና መገምገም ሥራዎች ይገኙበታል፡
  7. ዘመናዊ የበጀት አስተዳደር የሂሳብ አያያዝ፣ የግዥና የንብረት አስተዳደር ስርዓት መመስረት፣በስራ ላይ መዋሉን መከታተልና መቆጣጠር፤
  8. የክልሉን መንግስት የፋይናንስና ንብረት ኢንስፔክሽን ማከናወን፣ እርምጃ መውሰድና እንድወስድ ማድረግ፤
  9. የክልሉን መንግስት የገቢ ደረስኝ ማሳተም፣ ማሰራጨት፣መከታተልና መቆጣጠር
  10. በክልሉ የሚገኙ የመንግስት ልማት ድርጅቶችን እንቅስቃሴና ተግባራት መከታተል፣ መቆጣጠርና አፈጻጸሞችን መገምገም
  11. ዓላማውን ለመፈጸም የሚረዱ ሌሎች ሥራዎችን ማከናወን ተግባራቶች ናቸው፡፡