• +251462204629
  • Hawassa , Ethiopia

የደቡብ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት የሚሆን ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ

አረመኔው የህወሃት አሸባሪ ቡድን በሰሜን ዕዝ መካላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ያደረሰውን እኩይ ተግባር ለመመከት የሚደረገው ህግን የማስከበርና የህልውና ዘመቻ በመደገፍ የቢሮው አመራሮችና ሠራተኞች ወደ 500 ሺህ ብር ድጋፍ አደረጉ።ለመከላከያ ሠራዊት የሚደረገውን የድጋፍ መርሀ-ግብር ምላሽ ለመሰጠት መላው የቢሮው አባላት ባደረጉት ውይይት ከወር ደመወዛቸው የሚቆረጥ የገንዘብ ድጋፍ ከመስጠት ባሻገር ማናቸውንም ጥሪ በመቀበል የህይወት መስዋዕተትነት እስከመክፈል ድረስ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል ።አያይዘውም ለሀገር ጋሻና መከታ በሆነው ሠራዊት ላይ አሸባሪው የወያኔ ቡድን የፈጸመውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እጅጉን እንደሚቃሙና ይህን አጸያፊ ተግባር መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈፀመው ከዲው ቡድን ለፍርድ እንዲቀርብ ጠይቀዋል።

0

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *