መግቢያ

የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ
የአቶ ተፈሪ አባተ መልዕክት
እንኳን ወደ ደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ድረገፅ በሰላም መጣችሁ፡፡
ቢሮው የክልሉን የፊስካል ፖሊሲ አተገባበር ማዕቀፍ ማዘጋጀትና መተግብር፣ የክልሉን መንግስት በጀት ማዘጋጀትና ማስተዳደር፣ በተፈቀደው በጀት መሠረት ክፍያ መፈጸም፣ የበጀቱን አፈጻጸም መከታተል፤ የክልሉ መንግስት የበጀት፣ የሂሳብ፣ የክፍያና ጥሬ ገንዘብ እና የውስጥ ኦዲት ሥርዓት መዘርጋትና በስራ ላይ እንዲውል ማድረግ፣ የክልሉን መንግስት የገንዘብ ሰነዶች፣ ገንዘብና ንብረቶች መያዝና ማስተዳደር፣የክልሉ መንግስት የብድርና እርዳታ ስምምነቶችን መፈራረምና ከአጋር ድርጅቶች የሚገኘውን ሀብት ውጤታማና በተቀላጠፈ አኳኋን ማስተዳደርና አፈጻጸሙን መከታተል፣ የክልሉን መንግስት የፋይናንስና ንብረት ኢንስፔክሽን ማከናወን፣ ዘመናዊ የበጀት አስተዳደር፤ የሂሳብ አያያዝ፣ የግዥና የንብረት አስተዳደር፣ በኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ማስተባበርና መቆጣጠር፤ ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የቅድመ ስምሪት የስራ ውል ፈቃድ መስጠት፣ አተገባበራቸውንም በመስክ የመከታታልና የመገምገም እንዲሁም የሀብት ፍሰትና ስርጭት ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ማስቻል፣ በክልሉ የሚገኙ የመንግስት ልማት ድርጅቶችን እንቅስቃሴ ትርፋማነታቸውንና የገበያ ትስስራቸውን መከታተል፣ መቆጣጠርና አፈጻጸሞችንም በመገምገም ግብረ-መልስ መስጠትና ማስተካከያዎችን ማድረግ፣ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሠረት በበላይነት የመምራት ዋና ኃላፊነት አለበት፡፡Read More
በ2012 የኢትዮጵያ የነፍስ ወከፍ ገቢ 953.18 ዶላር ከነበረበት በ2022 ወደ 2,220 ዶላር ለማድረስ የተያዘውን ግብ በክልላችን ለማሳካት በሚደረገዉ ርብርብ ወሳኙን ምዕራፍ የያዘ ሲሆን፣ በክልላችን በብልፅግና ጉዞ የዜጎችን ቁሳዊ ፍላጎት፣ ዕኩል የልማት ተሳታፊነት፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ነፃነትን ለማረጋገጥ የክልሉን ሀብት በብቃት በማሰተዳደርና ቀጣይነት ያለው ሁለን አቀፍ ልማት በማረጋገጥ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ለውጥ መጥቶ ማየት፣ በክልላችን ፐብሉክ ሰርቪሱ ዉስጥ በሌህቀቱና በውጤቱ መሪ ተቋም መሆን፤
በቁጠባ ላይ የተመሰረተ የሀብት አጠቃቀም እንዲሰፍን የተቋሙን አቀም ግንባታ በማከናወን ፣ ዘመናዊ የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደርና ቁጥጥር ስርዓትን በመዘርጋት፣ የፊስካል ፖሊሲ፣ሲቪክና ትብብር ሀብት በማስተባበርና በመምራት፣ የመንግስት ልማት ድርጅቶችን በማስተባበር፣ አሰራሩን የጠበቀ ግዥ ሥራዓት በመዘርጋት እና የንብረት ማስወገድ ሥራዎችን በማካሄድ ፣ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አኳኋን በክልሉ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ፍትሃዊ ሀብት አሰተዳደር በላቀ ደረጃ ተግባራዊ እንዲሆን ::
- የሕዝብ አገልጋይነት፣
- ዉጤታማነት፣
- የስራ ትጋትና ቁርጠኝነት፣
- ህጋዊነት፣
- የሙያ ልቀት፣
- የመማሪና የለውጥ ተነሳሽነት፣
- ተጋግዝ በቡድን መሥራት፤
- የበለፀገ ኢኮኖሚ መገንባት
የተቋሙ ስልጣንና ተግባር
- የክልሉን መንግስት በጀት ማዘጋጀት፣ በተፈቀደው በጀት መሠረት ክፍያ መፈጸም፣ የበጀቱን አፈጻጸም ማስተዳደር፣ መገምገምና መቆጣጠር፤
- የክልሉ መንግስት የበጀት፣የሂሳብ፣የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥራዓት መዘርጋትና በስራ ላይ እንዲዉል ማድረግና መከታተል፤
- የክልሉን መንግስት የገንዘብ ሰነዶች፣ ገንዘቦችና ንብረቶች መያዝና ማስተዳደር፣
- የክልሉ መንግስት የብድርና እርዳታ ስምምነቶችን መፈራረምና ማስተዳደር፤
- በኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ስራ ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ማስተባበርና መቆጣጠር፤
- የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች የብቃት ምዘና ማድረግ፣ የስራ ውል መፈራረም፣ ማስተባበር፣ መከታታልና መገምገም ፣
- ዘመናዊ የበጀት አስተዳደር የሂሳብ አያያዝ፣ የግዥና የንብረት አስተዳደር ስርዓት መመስረት፣ በስራ ላይ መዋሉን መከታተልና መቆጣጠር፤
- የክልሉን መንግስት የፋይናንስና ንብረት ኢንስፔክሽን ማከናወን፣ እርምጃ መውሰድና እንድወስድ ማድረግ:
- የክልሉን መንግስት ህተመቶችን ማሳተም፣ ማሰራጨት፣መከታተልና መቆጣጠር
- በክልሉ የሚገኙ የመንግስት ልማት ድርጅቶችን እንቅስቃሴና ተግባራት መከታተል፣ መቆጣጠርና አፈጻጸሞችን መገምገም
- ዓላማውን ለመፈጸም የሚረዱ ልሎች ሥራዎችን ማከናወን ፡፡